የ17 ዓመቱ አታላህ ሙሐመድ በወታደሮቹ ላይ በስለት ታግዞ ጥቃት ሊየደርስ ሲል ነው የተገደለው፡፡ በዌስት ባንክ በሚገኝ ኤሪዬል በተባለ የሰፈራ አካባቢ የተፈጠረው የጥቃት ሙከራና ግድያ በፍልስጤም ባለስልጣናት የተረጋገጠ ነው፡፡
ሆኖም ወጣቱ መሳሪያ የታጠቁ ወታደሮችን በስለት ለማጥቃት የሄደበት ርቀት አለመረጋገጡ ቁጣን ቀስቅሷል፡፡ በእርግጥ የእስራኤል ወታደሮች ከዚህ በፊት በርካታ የጥይትና የስለት ጥቃቶች ሲደርሱባቸው እንደቆዬ ይነገራል፡፡ጥቃት አድራሾቹም በህገ-ወጥ ሰፈራዎች ምክንያት የሚበሳጩ ወጣት ፍልስጤማውያን ናቸው፡፡
የፍልስጤምና የእስራኤል የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ግን ዛሬም ድረስ ከተገቢው በላይ የሆነ ሃይልን ይጠቀማል በሚል የእስራኤልን መንግስት እንደሚከሱ አሶሼትድ ፕሬስ ዘግባል፡፡
************************************************************************
ቀን 19/05/2013
አሐዱ ራዲዮ 94.3