15.6 C
Ethiopia
Friday, March 29, 2024

ከበጎ ፍቃድ አገልግሎት ጋር በተያያዘ እስካሁን የጎላ ችግር ባያጋጥምም የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ መዘጋጀቱ ግን አስፈላጊ ነው ተባለ፡፡

በትናንትው ዕለት ረቡዕ ጥር 19 ቀን 2013 ዓ/ም የኢትዮጵያ ስራ አመራር ኢኒስቲትዩት እና የአዲስ አበባ ወጣቶችና በጎ ፍቃድ ቢሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ለመስራት ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡በስምምነታቸው መሠረት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በመጪዎች አስር ዓመታት የሚመራበት ፍኖተ ካርታ በቀጣይ ሁለት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል የሚለው ይገኝበታል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በአዲስ አበባ የሚካሄዱ የበጎ አድራጎት ስራዎችን ህጋዊ ሰውነት ለማላበስ በሚል የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡መመሪያው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት የገለጹት የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና በጎ ፍቃድ ምክትል ቢሮ ሐላፊ አቶ ፍሰሃ ጥበቡ ናቸው፡፡

አሐዱ በዚህ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት እስካሁን ምን ዓይነት እክሎች ስላገጠሙ ነው መመሪያው ያስፈለገው ሲል ምክትል ቢሮ ሐላፊውን ጠይቋል፡፡ሐላፊው ምንም እንኳን በዝርዝር ሊቀመጥ የሚችል ችግር ባያጋጥምም የመመሪያው መዘጋጀት አስፈላጊነት ግን አያጠያይቅም ብለዋል፡፡

*******************************************************

ቀን 20/05/2013

አሐዱ ራዲዮ 94.3

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

LIVE OFFLINE
Loading...