12.5 C
Ethiopia
Friday, March 29, 2024

የውስጥ የፀጥታ ችግሮቻችንን በፍጥነት በመፍታት ግብፅ በቀጣይ ለምትሰነዝራቸው እያንዳንዱ አሉታዊ ጉዳዮች ምላሽ ለመስጠት ከፍተኛ ዝግጅት ያስፈልጋል ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሳሰቡ፡፡

የእናት ፓርቲ ዋና ፀሐፊ አቶ ጌትነት ወርቁ ለአሐዱ እንዳሉት ግብፅ በየጊዜው ለምታወጣው መረጃ ኢትዮጵያ ማፈግፈግ የለባትም፤ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ሁሉን አቀፍ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡

አክለውም በሀገሪቷ ውስጥ የሚስተዋሉ የፀጥታ ችግሮችን በፍጥነት በመፍታት ግብፅ በቀጣይ ለምትሰነዝራቸው ሴራዎች ምላሽ ለመስጠት ከፍተኛ ዝግጅት እንደሚያስፈልግ ዋናው ፀሐፊው ገልፀዋል፡፡

በሀገር ውስጥ የሚስተዋሉትን የፀጥታ ችግሮች መፍታት ከተቻለ ግብፅ በየጊዜው ለምታነሳቸው ፕሮፓጋንዳዎች ኢትዮጵያ ለመቋቋም እንደማይከብዳት የሚያነሱት ደግሞ የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ኅብረት ሊቀ-መንበር አቶ ገብሩ በርሄ ናቸው፡፡

ቀን 06/08/2013

አሐዱ ራድዮ 94.3

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

LIVE OFFLINE
Loading...