12.7 C
Ethiopia
Thursday, March 28, 2024

በህገ-ወጥ መልኩ ሲዘዋወር የተገኘ 13 ሺ 588 ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን አስታወቀ፡፡

በስምንት ወራት ውስጥ በህገ-ወጥ መልኩ ሲዘዋወር የተገኘ የተለያየ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉን ኮምሽኑ አስታውቋል፡፡የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ፋሲካ ፍንታ ለአሐዱ እንደተናገሩት ከተማ ውስጥ ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያና የገንዝብ ዝውወር ተበራክቷል፡፡

ህገ-ወጥ የመሳሪያ ዝውውርን ለመቆጣጠር ከመረጃ መረብ ደህንነት አገልገሎት፣ ከፌደራል ፖሊስ እንዲሁም ከማህበረሰቡ ጋር በጋራ በመሆን አደጋ ሳያደርሱ በቁጥጥር ስር ማዋል እንደተቻለም ገልጸዋል፡፡

በስምንት ወራት ውስጥም 3 ብሬን ጠመንጃ፣ 288 የተለያዩ ሸጉጦች፣ 100 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 5 ቦንቦች፤ 12 ሺ 796 የሸጉጥ ጥይት፣ እንዲሁም ሌሎች መሳሪያዎች በአጠቃላይ 13 ሺ 588 የጦር መሳሪያ ጥይቶች መያዛቸውን ተናግረዋል፡፡

በተሽከርካሪ ውስጥ በሚደረግ ፍተሻ በቦቲ ውስጥ እንዲሁም ህጻናት በሚጫወቱበት ቦታዎች ላይ የተጣሉ በህብረተሰቡ ጥቆማ መያዛቸውን ተናግረዋል፡፡በህገ-ወጥ የመሳሪያ ዝውውር ባለፉት 8 ወራት 586 መዝገብ የተከፈተ ሲሆን ፤ 701  ተከሳሶች በአጠቃላይ 686 ወንጀለኞች መያዛቸውን የተናገሩት ኮማንደር ፋሲካ 15 የሚሆኑት አንዳልተያዙ አስታውቀዋል፡፡

ፖሊስ ኮምሽኑ ያልተያዙትን ህገ-ወጦች ለመያዝ እየሰራ ሲሆን ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለማስቆም ከሚመለከታቸው አካላትና ከማህበረሰቡ ጋር በጋራ በመሆን እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ቀን 08/08/2013

አሐዱ ራድዮ 94.3

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

LIVE OFFLINE
Loading...