ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ብሔራዊ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን፤ በአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ዙሪያ ከተለያዩ ረጂ ተቋማት የሚወጡ መረጃዎች መሬት ላይ ካለው ሀቅ ጋር አይገናኙም ሲል ለአሐዱ ገልጿል።
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ሕገወጥ የነዳጅ ግብይትን ይገታል የተባለለት ከ 300 ሺሕ እስከ 700 ሺሕ ብር የገንዘብ መቀጮ ያለው ሕግ ወጥቶ፤ ባለፈው ሳምንት ጀምሮ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታውቋል።
👉 "ከደረሰኝ ጋር ቁጥጥር እያደረገ የሚገኘው ገቢዎች ቢሮ ነው" ንግድ ቢሮ
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከተለያዩ ፓርቲዎች የሰበሰበውን ወደ 7 የሚሆኑ ዋና አጀንዳዎችንና 64 የሚሆኑ ንዑስ አጀንዳዎችን ሰብስቦ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክቧል።
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ2017 ሁለት ወራት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 6 ማደያዎች ላይ እርምጃ ሲወሰድ ሁለት ማደያዎች በጊዜያዊነት ሥራ ማቆማቸውን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታውቋል።
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በደቡብ ኢትዮጵያ በጋሞ ዞን የሚገኘው የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ አዋሳኝ አካባቢ የሚኖሩ ማሕበረሰቦች ወደ ፓርኩ ዘልቀው በመግባታቸው እና በፓርኩ ውስጥ የሚገኘው የዱር እንስሳት አደን በመደረጉ ፓርኩ ስጋት ላይ መሆኑ በተደጋጋሚ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ ያለዉ የዋጋ ንረት በሚቀጥሉት ወራት ከነበረዉ 16 ነጥብ 1 በመቶ በ10 በመቶ ጨምሮ፤ 26 ነጥብ 1 በመቶ ሊደርስ እንደሚችል የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር ያወጣው የፖሊሲ ጥናት አመላክቷል።
ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ኢትዮጵያ ውስጥ ከአስር ሴቶች መካከል አንዷ አካላዊ ጥቃት እንደሚደርስባት የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ አስታውቋል።
ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የሚገኝ አንድ በርበሬ ከባዕድ ነገር ጋር ተቀላቅሎ የሚመረትበት መጋዘን ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገልጿል።
ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኦሮሚያ ክልል መንግሥት እና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አመራሮች የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ፤ የሠራዊቱ አባላት ወደ ተዘጋጀላቸው ካምፕ መግባት መጀመራቸው ተገልጿል፡፡
ኤፍ ኤም 94.3