የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔውን ትላንት ያካሄደ ሲሆን የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫን ጨምሮ በአራት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ አፅድቋል።
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የቀድሞ ተዋጊዎችን ወደ ማህበረሰቡ ለመቀላቀል እየተሰራ ያለው ሥራ መቀጠሉን የገለጸው የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን፤ በትግራይ ክልል ወደ ማህበረሰቡ ለመቀላቀል ካሰባቸው 70 ሺሕ በላይ የቀድሞ ተዋጊዎች መካካል 2 ሺሕ ገደማ የሚሆኑት በማዕከሉ ስልጠና መውሰዳቸውን ገልጿል፡፡
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ብሔራዊ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን፤ በአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ዙሪያ ከተለያዩ ረጂ ተቋማት የሚወጡ መረጃዎች መሬት ላይ ካለው ሀቅ ጋር አይገናኙም ሲል ለአሐዱ ገልጿል።
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ሕገወጥ የነዳጅ ግብይትን ይገታል የተባለለት ከ 300 ሺሕ እስከ 700 ሺሕ ብር የገንዘብ መቀጮ ያለው ሕግ ወጥቶ፤ ባለፈው ሳምንት ጀምሮ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታውቋል።
👉 "ከደረሰኝ ጋር ቁጥጥር እያደረገ የሚገኘው ገቢዎች ቢሮ ነው" ንግድ ቢሮ
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ኢትዮጵያ የንጥረ ነገር እጥረት በጤና ላይ የሚያስከትለውን ችግር ለማከም እና ለመርዳት ብቻ፤ በዓመት ከአጠቃላይ ኢኮኖሚው ላይ 5 ቢሊየን ዶላር እንደምታጣ ሚለር ፎር ኒውትሬሽን ኢትዮጵያ ገለጸ።
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በቅርቡ የኤርትራዉ ፕሬዘዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከሀገራቸዉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር በነበራቸዉ ቃለመጠይቅ፤ "ዋናዉ ትኩረታችን ሁሌም ጦርነትን ማስወገድ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል።
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከተለያዩ ፓርቲዎች የሰበሰበውን ወደ 7 የሚሆኑ ዋና አጀንዳዎችንና 64 የሚሆኑ ንዑስ አጀንዳዎችን ሰብስቦ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክቧል።
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ2017 ሁለት ወራት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 6 ማደያዎች ላይ እርምጃ ሲወሰድ ሁለት ማደያዎች በጊዜያዊነት ሥራ ማቆማቸውን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታውቋል።
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በደቡብ ኢትዮጵያ በጋሞ ዞን የሚገኘው የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ አዋሳኝ አካባቢ የሚኖሩ ማሕበረሰቦች ወደ ፓርኩ ዘልቀው በመግባታቸው እና በፓርኩ ውስጥ የሚገኘው የዱር እንስሳት አደን በመደረጉ ፓርኩ ስጋት ላይ መሆኑ በተደጋጋሚ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡
ኤፍ ኤም 94.3