ቻይና ማስጠቀቂያዉን ለማዉጣት የተገደደችዉ፤ አሜሪካ ባሳለፍነው ቅዳሜ 385 ሚሊዮን ዶላር የሚገመቱ ኤፍ 16 የጦር ጄቶች እና መለዎወጫዎችን ለታይዋን ለመሸጥ መወሰኗን ተከትሎ መሆኑ ተነግሯል።
"የአሜሪካ ያልተገናዘበ እና መርህን የጣሰ ዉሳኔ የአንድ ቻይናን ፖሊስ የሚጥስ ስለሆነ ቤጂንግ አትጋስም" ሲሉ የቻይና የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስጠንቅቀዋል።
"ዋሽንግተን ታይዋን የቻይና አንድ አካል መሆኗን መቀበል አለባት" ሲሉ ያሳሰቡት ሚኒስትሩ፤ "ይህን አሜሪካ በዝምታ የምታልፈዉ ከሆነ ግን ቻይና ሉአላዊነቷን ለማስጠበቅ ቁርጠኛ ናት" ማለታቸውን ኢንዲያን ታይምስ ዘግቧል።
ነገር ግን እራሷን እንደ ሉዓላዊ ሀገር የምትቆጥረዉ ታይዋን፤ ለኢኮኖሚ እድገት በጣም ወሳኝ በሆነ ግዛት ውስጥ እንደምትገኝ ተነግሯል።
በተጨማሪ ወደ ደሴቷ አሜሪካ የምትቀርብ ከሆነ ከምዕራብዊያን አጋሮቿ ጋር ጥብቅ የሆነ ትስስር ይፈጥርላታል ነዉ የተባለዉ።
አሜሪካ በታይዋን ጉዳይ ላይ ጣልቃ ከመግባት እንድትታቀብ ቻይና አስጠነቀች
ሕዳር 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) አሜሪካ በታይዋን ጉዳይ ላይ ጣልቃ ከመግባት መታቀብ አለባት ሲል የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስጠንቅቋል፡፡