"የኮማንዶዎቹ መመረቅ ዋናኛ አላማ የአልሸባብን ጥቃት ለመመከት ነው" ሲል በተርኪ የሶማሊያ ኢምባሲ አስታውቋል።

በሶማሊያ እና በቱርክ መካከል ያለውን ጠንካራ ግንኙነት በሁሉም መስክ ለማሳደግ እና ወንድማማችነትን የበለጠ ለማጠናከር ሞቃዲሾ በቁርጠኝነት መሥራቷን እንደምትቀጥል የሶማሊያ የመከላከያ ሚኒስትር አብዱልቃድር መሀመድ ኑር አስታዉቀዋል።

አክለውም፤ አንካራን "በተለይ ለሶማሊያ ሰላም እና ደህንነት እንዲሁም በአጠቃላይ ለምስራቅ አፍሪካ ለሚያደርገው ጠቃሚ ድጋፍ" ማመስገናቸውን አናዶሎ ዘግቧል።

ተርኪዬ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከሶማሊያ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እያጠናከረች ሲሆን፤ የትምህርት፣ የመሰረተ ልማት እና የጤና አጠባበቅ ዘርፎች ላይ ኢንቨስት አድርጋለች።