ጥር 6/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የእድሳት ሥራ ተጠናቆ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ቡራኬ በዛሬው ዕለት ተመርቋል፡፡

Post image

በአሁኑ ሰዓትም ታቦተ ሕጉ ጥንታዊነቱን ጠብቆ ወደ ታደሰው ካቴድራል በመግባት ላይ ይገኛል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት መምሪያ ኃላፊዎችና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ኃላፊዎች፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ ምዕመናን እና ምዕመናት ተገኝተዋል።

Post image

ከሁለት ዓመት በላይ በዕድሳት ላይ የቆየው የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ጥንታዊነቱን እንደጠበቀ መልኩ ዕድሳት እንደተደረገለት ተጠቁሟል።

ከተመሰረተ ከ81 ዓመታት በላይ የቆጠረው የመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እድሳት፤ ከ125 ሚልየን ብር በላይ በሆነ ወጪ መከናወኑን አሐዱ መዘገቡ ይታወሳል፡፡